የአስተዳደር ሰራተኞች ውይይት

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር ሰራተኞች በዩኒቨርሲቲው የ2011 ዓ.ም. ዕቅድ አፈፃፀምና የ2012 ዓ.ም. ዕቅድ ዙሪያ እየተወያዩ ነው።
በውይይቱ የሳይንስ ኮሌጅ፣ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ እንዲሁም የማሪታይም አካዳሚና ዋናው ግቢ አስተዳደር ሰራተኞች ተሳታፊ ሲሆኑ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮችም ተገኝተዋል። የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ጉዳዮች ም/ፕሬዚዳንት አቶ ብርሀኑ ገድፍ የዩኒቨርሲቲውን የ2011 ዓ.ም ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ካቀረቡ በኋላ በፕሬዚዳንቱ ዶ/ር ፍሬው ተገኘ አወያይነት ሰራተኛው እየተወያየ ነው።ይህ ውይይት ከሌሎች ግቢዎች አስተዳደር ሰራተኞች ጋርም በመጪዎቹ ቀናት የሚቀጥል ይሆናል።